የአውራ አምባ ማኅበረሰብ እምነት፣ ብሔርና የፖለቲካ አመለካከት አንድ ሆነን ከመኖር እንደማያግዱን ህያው ምስክር ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 21 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) እምነት፣ ብሔርና የፖለቲካ አመለካከት አንድ ሆነን ከመኖር እንደማያግዱን የአውራ አምባ ማኅበረሰብ ህያው ምስክር ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ የአውራ አምባ ማኅበረሰብ የጾታ እኩልነት፣ የሕጻናትና የአካል ጉዳተኞች ማኅበራዊ ፍትሕ በተግባር ተፈትኖ ያየንበት ነው ብለዋል።
ለሃምሳ ዓመታት በእነዚህ ዕሴቶች ጸንቶ መኖር ድንቅ ብቻ ሳይሆን ተአምርም ነው ሲሉም አስታውቀዋል።
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!