Fana: At a Speed of Life!

የፕሪሚየር ሊጉ አሸናፊ 1 ሚሊየን ብር ሽልማት ይበረከትለታል

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 7 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2013 ቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ የሚሆነው ክለብ የ1 ሚሊየን ብር ተሸላሚ እንደሚሆን የፕሪሚየር ሊጉ አክሲዮን ኩባንያ አስታወቀ፡፡

ኩባንያው ዛሬ በሰጠው መግለጫ ሁሉም ተሳታፊ ክለቦች እንደየ ደረጃቸው ሽልማት የሚበረከትላቸው ሲሆን፥ ሁለተኛ ሆኖ ለሚያጠናቅቅ ክለብ የ700 ሺህ እንዲሁም 3ኛ ሆኖ ለሚጨርስ የ500 ሺህ ብር ሽልማት እንደሚሰጥ ገልጿል።

የፕሪሚየር ሊጉ መርሃ ግብር ሳይጠናቀቅ አሸናፊው ከታወቀ ዋንጫው ለአሸናፊው ቀድሞ እንደሚሰጥ የኩባንያው ውድድር ሰብሳቢ መቶ አለቃ ፈቃደ ማሞ ተናግረዋል።

ፕሪሚየር ሊጉ ግንቦት 18 የሚጠናቀቅ ሲሆን፥ ግንቦት 21 ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ የኮኮቦች ሽልማት ይሰጣልም ብለዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.