ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በአማራ ክልል 5 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የሚደረግባቸው የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ አስጀመሩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአማራ ክልል 5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚደረግባቸው የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ አስጀመሩ፡፡
የአስፓልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታው ከዱር ቤቴ ቁንዝላ-ሻሁራ-ፍንጅት ምዕራፍ አንድና ከገላጎ -ገንዳ ውሀ ምዕራፍ ሶስት ነው የሚካሄደው፡፡
የመንገድ ርዝመቱ 260 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መሆኑም ተገልጿል፡፡
ከዱር -ቤቴ -ቁንዝላ ሻውራ -ፍንጅት ያለው የአስፓልት መንገድ ግንባታ 135 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን ከገላጎ ገንዳ ውሀ የአስፓልት መንገድ ግንባታ ደግሞ 125 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ነው።
የመንገዶቹ ግንባታ ወጭ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው ተብሏል፡፡
የመንገዶቹ ግንባታ በቻይናው ዚ-ዥ-ያንግ ኮሙዩኒኬሽን ኮንስትራክሽን ግሩፕ ይከናወናል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!