Fana: At a Speed of Life!

ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የተከለከሉ የእጅ ንጽህና መጠበቂያዎች

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 25 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ሳይመዘገቡና የብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ ሳያገኙ የተለያዩ ግለሰቦችና ተቋማት በህገ ወጥ መልኩ የእጅ ንጽህና መጠበቂያ (Hand sanitizers) ነው በማለት አምርተው ገበያ ላይ እያቀረቡ በመሆናቸው ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጠየቀ።

ባለስልጣኑ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት የምግብና መድኃኒት አስመጪዎች፣ አከፋፋዮችና አምራች ድርጅቶች የብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ እንደሚሰጥ ይታወቃል።

በአሁኑ ወቅት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚያስፈልጉ የእጅ ንጽህና መጠበቂያ ምርቶች በህጋዊ መንገድ በስፋት ተመርተው ገበያ ላይ እንዲቀርቡ ጊዜያዊ ፍቃድ በመስጠት ላይ ይገኛል።

ይሁን እንጅ በተደረገው የገበያ ጥናትና ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሳይመዘገቡና የብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ ሳያገኙ የተለያዩ ግለሰቦችና ተቋማት በህገ ወጥ መልኩ የእጅ ንጽህና መጠበቂያ (Hand sanitizers) አምርተው ገበያ ላይ እያቀረቡ መሆናቸውን አስታውቋል።

በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የእጅ ንጽህና መጠበቂያዎች በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ያልተመዘገቡና የብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ ያላገኙ እንዲሁም ጥራታቸውና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ በመሆናቸው ከገበያ እንዲሰበሰቡና ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው አሳስቧል።

Mela Sanitizer

Narobi Sanitizer

Habesha Sanitizer

FOM Sanitizer

GST Sanitizer

Silva Sanitizer

Yero Hand Sanitizer

Adey Hand Sanitizer

Abyssinia Hand Sanitizer

TAFF አልኮል

መሆናቸውን በማሳወቅ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ በማድረግ መሰል ምርቶች ሲያገኝ በአቅራቢያው ለሚገኝ የጤና ተቆጣጣሪ፣ ለፖሊስ አካላት ወይም በፌደራል ደረጃ ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በነጻ የስልክ መስመር በ8482 በመጠቆም እንዲያሳውቅም ጠይቋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.