1ሺህ 126 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ በሦስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ ዓረቢያ የመመለስ ሥራ 1 ሺህ 126 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ከተመለሱት ውስጥ ስድስቱ ሕጻናት መሆናቸውም ተመላክቷል፡፡
ለተመላሽ ዜጎችም ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማዕከላት እንዲሄዱ መደረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
እስካሁን ድረስ በተከናወነ ዜጎችን የመመለስ ሥራ ከ38 ሺህ 853 በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!