Fana: At a Speed of Life!

536 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ4 ሰዎች ህይወት አልፏል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 6 ሺህ 538 የላቦራቶሪ ምርመራ 536 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል ።
በዚህም በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 92 ሺህ 229 ደርሷል።

በሌላ በኩል በ24 ሰዓታት 858 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን በዚህም ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 46 ሺህ 118 ደርሷል።

እንዲሁም ከቫይረሱ ጋር ተያይዞ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉ የተገለፀ ሲሆን በአጠቃላይ በኢትዮጵያ እስካሁን በቫይረሱ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር 1 ሺህ 400 መድረሱ ተጠቁሟል።

315 ያህል ሰዎች ደግሞ በጽኑ ሕክምና ላይ መሆናቸውም ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.