Fana: At a Speed of Life!

ባለሃብቱ አቶ ሰይድ ዳምጠው የመቶ አለቃ ጌታቸው ሞሮዳን ልጅ ለማሳደግ ቃል ገቡ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 13 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለሃብቱ አቶ ሰይድ ዳምጠው የሀገርን ህልውና በማስከበር ዘመቻው መስዋዕት የሆነውን የመቶ አለቃ ጌታቸው ሞሮዳን ልጅ (ቢኒያም ጌታቸውን) ለመደገፍ 500 ሺህ ብር በመለገስ በኦሮሞ የገዳ ስርዓት መሰረት ልጃቸው አድርገው ለማሳደግ ቃል ገብተዋል፡፡

ይህ ስነ-ስርአት አዲስ አበባ በሚገኘው የኦቢኤን ስቱዲዮ የተከናወነ ሲሆን÷ የኦቢኤን ማኔጅመንት በበኩሉ ለታዳጊው የ200 ሺህ ብር ድጋፍ ማበርከቱን የኦቢኤን ዋና ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ዝናቡ አስራት ገልፀዋል።

በተጨማሪም ተቋሙ ቢኒያም ጌታቸውን የኦቢኤን ”ጋሜ” ቤተሰብ በማድረግ ተገቢውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግለት ገልፀዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.