Fana: At a Speed of Life!

በአፍሪካ እስካሁን ከ9 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ሰዎች በኮቪድ-19 ተይዘዋል

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ እስካሁን ከ9 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተገለጸ፡፡

ከ55 የአፍሪካ ሀገራት በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ከ9 ሚሊየን 505 ሺህ በላይ ሰዎች ሲደርሱ፥ በአህጉሪቱ ከ185 ሚሊየን 502 ሺህ በላይ ለሆኑ ሰዎች ክትባት መሰጠቱም ነው የተገለጸው፡፡

በአህጉሪቱ በቫይረሱ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥርም ከ227 ሺህ በልጧል፡፡

በአንጻሩ ከ8 ሚሊየን 508 ሺህ በላይ ሰዎች ከቫይረሱ ማገገማቸው ተነስቷል፡፡

ደቡብ አፍሪካ ከ3 ሚሊየን 417 ሺህ በላይ ሰዎች በኮሮና በመያዝ በቀዳሚነት ስትነሳ ፥ በአገሪቱ ከ90 ሺህ በላይ ሰዎች ለህልፈት ተዳርገዋል፡፡

ከደቡብ አፍሪካ በመቀጠል ሞሮኮ፣ ቱኒዚያ፣ ኢትዮጵያ፣ ሊቢያ፣ ግብጽ እና ኬኒያ ከአህጉሪቱ ቫይረሱ የጸናባቸው አገራት እንደሆኑም ነው የተገለጸው፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.