16ኛ ሳምንት ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ነገ በአዳማ ይጀምራል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 16ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕርሚየር ሊግ ነገ በሚካሄዱ መርሃግብሮች ይጀምራል፡፡
በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በሚደረገው ጨዋታ÷ 9 ሰዓት ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሰበታ ከተማ እንዲሁም 12 ሰዓት ላይ ደግሞ ፋሲል ከነማ ከሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታቸውን ያደረጋሉ፡፡
የስታዲየም የመግቢያ ዋጋን በተመለከተ 1ኛ ደረጃ ሁለት መቶ ብር፣ 2ኛ ደረጃ መቶ ብር እና 3ኛ ደረጃ መግቢያ 20 ብር መሆኑን ከቤት ኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!