Fana: At a Speed of Life!

የትራፊክ አደጋ አራት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለሙያዎችን ህይወት ቀጠፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሰራተኞች የነበሩ አራት ባለሙያዎች በመኪና አደጋ ህይዎታቸው አለፈ፡፡

ሰራተኞቹ በአማራ ክልል ደባረቅ ዞን ሳንቃ በር አከባቢ ልዩ ስሙ አበርጊና በሚባል ስፍራ ለመስክ ስራ ሲንቀሳቀሱ በደረሰባቸው የመኪና አደጋ ነው ሕይወታቸው ያለፈው፡፡

ይህንን ተከትሎም የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ሃዘናቸውን ገልጸው ፥ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.