ፋሲል ከነማ ቡማሙሩን 3 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ ፣ ጳጉሜን 4 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪከ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ቅድመ ማጣሪያ ከቡሩንዲው ክለብ ቡማሙሩ ጋር የተጫወተው ፋሲል ከነማ 3 ለ ዐ አሸንፏል።
በባህርዳር ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አለም ብርሃን ይግዛው፣ፈቃዱ አለሙ እና ታፈሰ ሰለሞን የማሸነፊያ ጎሎችን አስቆጥረዋል።
የሁለቱ ክለቦች የመልስ ጨዋታ መስከረም 6 ቀን የሚደረግ ይሆናል።