የዛሬ 7ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል
አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 1 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዛሬ 7ኛ ሳምንት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል::
በዚህም 10 ሰዓት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወልቂጤ ከተማ ባደረጉት ጨዋታ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስን ግቦች አማኑኤል ገብረሚካኤልና እስማኤል ኦሮ-አጎሮ ሲያስቆጥሩ የወልቂጤ ከተማን ሁለቱንም ግቦች አቡበከር ሳኒ አስቆጥሯል፡፡
በተመሳሳይ 1 ሰዓት ላይ ድሬዳዋ ከተማና መቻል ባደረጉት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
የመቻልን ግብ ያሬድ ታደሠ ሲያስቆጥር የድሬዳዋ ከተማን ግብ ሳሙኤል ሳሊሶ አስቆጥሯል፡፡