Fana: At a Speed of Life!

የምሁራንን ሐሳብ በማካተት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደሚገባ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀገር ግንባታ ሂደቱ የምሁራንን ሐሳብ በማካተት የተረጋጋችና ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደሚገባ ተገለጸ።

“በሀገር ግንባታ የምሁራን ድርሻ” በሚል መሪ ሐሳብ የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ሀገራዊ ችግር ፈቺና መፍትሔ ጠቋሚ ጉዳዮች ላይ የምሁራን ምክክር እያካሔደ ነው፡፡

የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ድረስ ሳኅሉ በመድረኩላይ ባደረጉት ንግግር÷ ኢትዮጵያውያን በሀገር ጉዳይ ላይ የጋራ አጀንዳ ሊኖረን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

በመሆኑም የተረጋጋችና የሰላም ግንባታ የሚታይባት ሀገር እንዲኖረን ምሁራን በመመካከር መፍትሔ ማምጣት አለባቸው ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.