ማሰን ማውንት ማንቼስተር ዩናይትድን ተቀላቀለ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ እንግሊዛዊውን አማካይ ማሰን ማውንትን በይፋ አስፈርሟል፡፡
የላንክሻየሩ ክለብ ማሰን ማውንትን በአምስት ዓመት ኮንትራት ነው ያስፈረመው፡፡
ለአማካዩ ዝውውር 60 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ መደረጉን ጠቅሶ ቢ ቢ ሲ ዘግቧል፡፡
ማውንት በቼልሲ ቆይታው 195 ጊዜ ተሰልፎ 33 ጎሎችን ማስቆጠሩ ይታወሳል፡፡