በፕርሚየር ሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታው አርሰናል ኖቲንግሀም ፎረስትን 2 ለ 1 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2023/24 የውድድር ዓመት በመጀመሪያ ሳምንት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የመጀመሪያ ጨዋታውን ከኖቲንግሀም ፎረስት ጋር ያደረገው አርሰናል 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የአርሰናልን የማሸነፊያ ግቦች ኤዲ ኒኪታህ እና ቡካዩ ሳካ ከመረብ ሲያሳርፉ÷ የኖቲንግሀም ፎረስትን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ ደግሞ አዎኒዪ አስቆጥሯል።
በቀጣይ ሳምንት መርሐ ግብር÷ አርሰናል ከክሪስታል ፓላስ ጋር ሲጫወት ኖቲንግሀም ፎረስት ሼፊልድ ዩናይትድን የሚገጥም ይሆናል።