በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለፍጻሜ አለፉ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሃንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ማጣሪያ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለፍጻሜ አለፉ፡፡
በ5ሺህ ሜትር ወንዶች ማጣሪያ ዮሚፍ ቀጀልቻ፣ ሀጐስ ገ/ሕይወት እና በሪሁን አረጋዊ ለፍፃሜ አልፈዋል፡፡
በሀንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ የሚገኘው 19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ስድስተ ቀኑን ይዟል፡፡