ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረ ማርያም ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ አቀረቡ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጊዜያዊ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረ ማርያም ከግብጽ ጋር ለሚደረገው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ጨዋታ ለ23 ተጨዋቾች ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በዚህ መሰረትም ፡-
በግብ ጠባቂነት፡- ሰኢድ ሃብታሙ፣ አቡበከር ኑራ እና ቢኒያም ገነቱ
በተከላካይ ስፍራ፡- ሄኖክ አዱኛ፣ አለምብርሃን ይግዛው፣ ሚሊዮን ሰለሞን፣ አስቻለው ታመነ፣ ምኞት ደበበ፣ አማኑኤል ተርፋ፣ ረመዳን የሱፍ እና ፍራኦል መንግስቱ፣
በመሃል ክፍል፡- ጋቶች ፓኖም፣ አማኑኡል ዮሃንስ፣ ሽምልስ በቀለ፣ ሱራፌል ዳኛቸው፣ ቢኒያም በላይ እና ወገኔ ገዛኸኝ፣
በአጥቂ መስመር፡- አቤል ያለው፣ ዳዋ ሁጤሳ ፣ ቸርነት ጉግሳ፣ ፍጹም ጥላሁን እና ሃብታሙ ታደሰ ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡
ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች ማክሰኞ ነሐሴ 23 ቀን ካዛንቺስ በሚገኘው ጁፒተር ሆቴል ተገኝተው ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ሪፖርት እንዲያደርጉ ፌዴሬሽን አሳስቧል፡፡
ጨዋታው የፊታችን ጳጉሜን 3 በግብጽ የሚደረግ መሆኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡