Fana: At a Speed of Life!

ንግድ ባንክ በምስራቅ አፍሪካ የቻምፒየንስ ሊግ ማጣሪያ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በምስራቅ አፍሪካ የቻምፒየንስ ሊግ ማጣሪያ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቋል፡፡

በውድድሩ ፍፃሜ የታንዛኒያውን ጀኬቲ ኩዊንስ የገጠመው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ÷ መደበኛ ጨዋታውን በአቻ ውጤት ማጠናቀቁን ተከትሎ ወደ መለያ ምት አምርተዋል፡፡

በዚህም 5 ለ 4 ተሸንፎ ዋንጫውን አጥቷል፡፡

ይህን ተከትሎም ኢትዮጵያን የወከለው ንግድ ባንክ ውድድሩን በሁለተኛነት ለማጠናቀቅ ተገዷል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም የምስራቅ አፍሪካ ሻምፒዮን የሆነው ጄቲኬ ኩዊንስ በአይቮሪኮስት አስተናጋጅነት በሚከናወነው ዋናው የቻምፒየንስ ሊግ ውድድር መሳተፉን አረጋግጧል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.