ንግድ ባንክ በምስራቅ አፍሪካ የቻምፒየንስ ሊግ ማጣሪያ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በምስራቅ አፍሪካ የቻምፒየንስ ሊግ ማጣሪያ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቋል፡፡
በውድድሩ ፍፃሜ የታንዛኒያውን ጀኬቲ ኩዊንስ የገጠመው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ÷ መደበኛ ጨዋታውን በአቻ ውጤት ማጠናቀቁን ተከትሎ ወደ መለያ ምት አምርተዋል፡፡
በዚህም 5 ለ 4 ተሸንፎ ዋንጫውን አጥቷል፡፡
ይህን ተከትሎም ኢትዮጵያን የወከለው ንግድ ባንክ ውድድሩን በሁለተኛነት ለማጠናቀቅ ተገዷል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም የምስራቅ አፍሪካ ሻምፒዮን የሆነው ጄቲኬ ኩዊንስ በአይቮሪኮስት አስተናጋጅነት በሚከናወነው ዋናው የቻምፒየንስ ሊግ ውድድር መሳተፉን አረጋግጧል።