ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በ5 ኪሎ ሜትር የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል ቀናቸው
አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶች 5 ኪሎ ሜትር የሪጋ የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል ቀንቷቸዋል፡፡
አትሌት ሀጐስ ገ/ሕይወ ርቀቱን 12 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ መሆን ችሏል፡፡
ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ደግሞ ርቀቱን በ13 ደቂቃ ከ02 ሰከንድ በማጠናቀቅ 2ኛ ደረጃን ይዟል፡፡
በተመሰሳሳይ ÷አትሌት እጅጋየሁ ታዬ በሴቶች የ5 ኪሎ ሜትር የሪጋ የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች፡፡
አትሌት እጅጋየሁ ርቀቱን 14 ደቂቃ ከ40 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ሶስተኛ ደረጃን የያዘችው፡፡