Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በ5 ኪሎ ሜትር የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶች 5 ኪሎ ሜትር የሪጋ የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል ቀንቷቸዋል፡፡

አትሌት ሀጐስ ገ/ሕይወ ርቀቱን 12 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ቀዳሚ መሆን ችሏል፡፡

ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ ደግሞ ርቀቱን በ13 ደቂቃ ከ02 ሰከንድ በማጠናቀቅ 2ኛ ደረጃን ይዟል፡፡

በተመሰሳሳይ ÷አትሌት እጅጋየሁ ታዬ በሴቶች የ5 ኪሎ ሜትር የሪጋ የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች፡፡

አትሌት እጅጋየሁ ርቀቱን 14 ደቂቃ ከ40 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ሶስተኛ ደረጃን የያዘችው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.