Fana: At a Speed of Life!

ድርቤ ወልተጂ በአንድ ማይል የሴቶች የጎዳና ላይ ሩጫ ሪከርድ ሰበረች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ድርቤ ወልተጂ በአንድ ማይል የሴቶች የጎዳና ላይ ሩጫ ሪከርድ በመስበር አሸነፈች፡፡

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሴቶች አንድ ማይል የሪጋ የዓለም የጎዳና ላይ ሩጫ ድል ቀንቷቸዋል፡፡

ርቀቱን አትሌት ድርቤ ወልተጂ በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ ፍሬወይኒ ኃይሉ ደግሞ ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች፡፡

ድርቤ ወልተጂ በ4 ደቂቃ ከ21 ሰከንድ በሆነም ነው የዓለምን ሪከርድ የሰበረችው፡፡

ሁለተኛ የወጣችው ፍሬወይኒ ኃይሉ 4 ደቂቃ ከ23 ሰከንድ ከ6ሚሊ ሰከንድ በሆነ 2ኛ መውጣቷን ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

እንዲሁም 7፡30 ላይ በተካሄደው የዓለም የጎዳና ውድድር የሴቶች የግማሽ ማራቶን አትሌት ጽጌ ገ/ሰላማ፣ ያለምጌጥ ያረጋል እና ፍታው ዘርዬ ኢትዮጵያን ወክለው ተሳትፈዋል፡፡
በዚህም አትሌት ጽጌ ገ/ሰላማ በ1:07:50 4ኛ ደረጃ በመያዝ፣ አትሌት ፍታው ዘርዬ ደግሞ በ1:08:31 6ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል፡፡
በላቲቪያ ሪጋ በተካሄደው የዓለም የጎዳና ላይ የሴቶች የግማሽ ማራቶን ውድድር ኬንያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አሸንፈዋል፡፡

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.