Fana: At a Speed of Life!

23 ነጥብ 1 ቢለየን ብር ለድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች ተከፈለ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች 23 ነጥብ 1 ቢለየን ብር በላይ መከፈሉን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

ባለሥልጣኑ በ2016 በጀት ዓመት መጀመሪያ ሩብ ዓመት÷ለነዳጅ ኮንትሮባንድ ሽያጭ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን 65 በመቶ መቀነስ መቻሉን አስረድቷል፡፡

ከተቀመጠው አሠራር ውጭ አገልግሎት በማይሰጡና ነዳጅ ሣይቀዱ የድጎማ ክፍያ ለሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች ትብብር በሚፈፅሙ 5 ነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ መውሰዱንም ጠቁሟል፡፡

እስከ ባለፈው መስከረም ወር መጨረሻ ድረስም 23 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር በላይ ለድጎማ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች መከፈሉን የባለስልጣኑ መረጃ ያመላክታል፡፡

በዚሁ መንገድ 120 ቢሊየን ብር በላይ ዋጋ ያለው የነዳጅ ግብይት የተፈጸመ ሲሆን÷የነዳጅ ስርጭት ቁጥጥርን ለማዘመን ነዳጅ ጫኝ ተሽከርካሪዎች ጂ ፒ ኤስ እንዲገጥሙ መደረጉ ተገልጿል፡፡

ማደያ በሌለባቸው 556 ወረዳዎች አዳዲስ ማደያዎች እንዲገነቡ በተቀመጠው ዕቅድ መሰረትም በ8 ወረዳዎች አዳዲስ ማደያዎች ተገንበተው የነዳጅ ትስስር ፈቃድ ማግኘታቸው ተጠቅሷል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.