Fana: At a Speed of Life!

የንግድ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት ለ10 ቀናት ተራዘመ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የንግድ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት ለቀጣዮቹ አሥር ቀናት መራዘሙን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በሲስተም መቆራረጥ እና ከክልሎች አወቃቀር ጋር በተያያዘ የንግድ ፈቃድ እድሳት ሂደቱ በመስተጓጎሉ ለሚቀጥሉት አሥር ቀናት ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱንም ነው ሚኒስቴሩ ያስታወቀው፡፡

አጋጣሚው ነጋዴዎች የንግድ ሥራ ፈቃድ እድሳት አገልግሎትን ያለ ቅጣት ማግኘት የሚችሉበት መሆኑም ተገልጿል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.