Fana: At a Speed of Life!

ሞሪታኒያ የ2024 አፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበርነትን ከኮሞሮስ ተረከበች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሞሪታንያው ፕሬዚዳንት ሞሃመድ ኦልድ ጋውዛኒ የ2024 የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር ሆነው ተመርጠዋል፡፡

37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ እየተካሄደ ነው፡፡

በጉባኤውም ሞሪታኒያ የሊቀመንበርነትን ቦታ የተረከበች ሲሆን ፥ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሞሃመድ ኦልድ ጋዙዋኒ በ2024 የአፍሪካ ሕብረትን በሊቀ መንበርነት ይመራሉ።

ትምህርት የሁለንተናዊ እድገት መሰረት መሆኑን በመድረኩ ባደረጉት ንግግር የገለፁት ፕሬዚዳንት ሙሃመድ ኡልድ ጋዙዋኒ ፥ የተማረ ሃይል የአህጉሪቱን ፈታኝ ችግሮች ለመቅረፍ ያስችለናል ብለዋል።

ለዚህም ያለውን ሃብት ለትምህርት መሰረተ ልማት ዝርጋታና መሰል ስራዎች ላይ ማዋል እንደሚገባም ነው የተናገሩት።

በተጨማሪም በአህጉሪቱ የሚከሰቱ ግጭቶችን ለመከላከል ወጣቱን ኃይል ወደትምህርትና ምርምር ማሰማራት እንደሚያስፈልግ ጠቅሰዋል።

ባለፈው ዓመት የኮሞሮስ ፕሬዚዳንት አዛሊ አሱማኒ የሕብረቱ ሊቀመንበር ሆነው ማገልገላቸው ይታወሳል።

በአሸናፊ ሽብሩ እና ሳሙኤል ወርቃየሁ

#Ethiopia #AU #Mauritania

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting/
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.