Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ በማዕድን ዘርፍ በጋራ ለመሥራት ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ኦስትሪያ ማዕድን ፍለጋን ጨምሮ ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተስማሙ፡፡

የማዕድን ሚኒስትር ሃብታሙ ተገኝ (ኢ/ር ) በኢትዮጵያ የኦስትሪያ አምባሳደር ሲሞን ኬናፕ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም ሁለቱ ሀገራት በማዕድን ፍለጋና ልማት፣ በአቅም ግንባታና ስልጠና፣ በቴክኖሎጂ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል፡፡

ሃብታሙ (ኢ/ር) በዘርፉ ያሉ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ለአምባሳደሯ ማብራራታቸውን የማዕድን ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

አምባሳደሯ በበኩላቸው የሀገራቸው የማዕድን ኩባንያዎች እና መንግሥታቸው ከኢትዮጵያ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች በጋራ እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.