Fana: At a Speed of Life!

አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የወደፊት የሀገራችን ችግር መፍቻ ቁልፍ ነው – ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የወደፊት የዓለማችን እና የሀገራችን ችግር መፍቻ ቁልፍ ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡

ደስታ የተሰኘች ሮቦት በኢትዮጵያ በመገኘት የሙዚቃ ዝግጅቷን ከአርቲስት ሙላቱ አስታጥቄ(ዶ/ር) ጋር እያቀረበች እንደምትገኝ ተገልጿል፡፡

በዝግጅቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እንዳሉት ፥ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በየጊዜው አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እያመጣ ኢትዮጵያን ከሌላው ዓለም እኩል እንድትጓዝ እየሰራ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡

አያይዘውም ፥ ኢንስቲትዩቱ የወደፊት የዓለም ተፅእኖ ፈጣሪ ታዳጊዎችን ለመፍጠር እየሰራ ያለውን ስራ በዲጂታል ኢትዮጵያ ምክር ቤት ስም ማስገናቸውን ከኢንስቲትዩቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.