Fana: At a Speed of Life!

የሐረሪ ክልል ገቢዎች ቢሮ ከ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ከ1 ቢሊየን 428 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የሐረሪ ክልል ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው ሃላፊ ወ/ሮ ኢክራም አብዱልቃድር ÷ ገቢው ከቀጥታ ታክስ፣ ቀጥታ ካልሆነ የታክስና ታክስ ነክ ካልሆኑ ገቢዎች እንዲሁም ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢዎች መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡

ገቢው ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ248 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር ብልጫ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡

ቢሮው የገቢ አሰባሰቡን የበለጠ ለማጎልበትና ሕገ-ወጥ ንግድን ለመዋጋት በዲጅታል የተደገፈ አሰራርን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.