ከንቲባ ከድር ጁሃር የትንሳኤ በዓልን በመደጋገፍ ማክበር እንደሚገባ ገለጹ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የትንሳኤ በዓልን ስናከብር የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህላችንን በማጠናከር ሊሆን ይገባል ሲሉ የድሬዳዋ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ።
ከንቲባው ለትንሳኤ በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መልዕክት÷ ለክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡
በዓሉን ስናከብርም ለችግር የተዳረጉ ሕጻናትና አረጋውያንን በመርዳት ሊሆን ይገባል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
የሰላም፣ የአንድነትና የልማት ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።