Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ የትራንስፎርሜሽናል ዕቅድ ዝግጅት መድረክ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች የተሳተፉበት የትራንስፎርሜሽናል ዕቅድ ዝግጅት መድረክ መካሄድ ጀመረ።

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በመድረኩ አዲስ አበባን ዓለም አቀፍ ተመራጭ ከተማ ለማድረግ በሚያስችሉ በተመረጡ ስድስት አጀንዳዎች ላይ ስልጠና እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

በዚህም የትራንስፎርሜሽን እቅድ ዝግጅት የሚከናወን ሲሆን በስልጠናው ዓለም አቀፍ የዘርፉ ባለሙያዎች ለአመራሩ ስልጠና እንደሚሰጡ ገልጸዋል።

ሀገራችንን ለማበልጸግ በሁሉም ዘርፍ ያለ እረፍት መስራታችን ተጠናክሮ ቀጥሏል ሲሉም በመልዕክታቸው አመልክተዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.