Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮ-አሜሪካ 120ኛ ዓመት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የሚያሳይ ዐውደርዕይ ተከፈተ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያና የአሜሪካን 120ኛ ዓመት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የሚያወሳ “120 ዓመታት የሁለትዮሽ ምስላዊ ጉዞ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ምስላዊ ዓውደ ርዕይ በይፋ ተከፍቷል።

በሁነቱ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ፥ ሁለቱ ሀገራት በትምህርት፣ በጤና፣ በኢኮኖሚ ለ120 ዓመታት የነበራቸውን ትብብር ወደፊትም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

የሀገራቱን የረጅም ዓመታት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ዓውደ ርዕዩ አጋዥ ምህዳር የሚፈጥር ነው ያሉት ደግሞ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ናቸው።

ዓውደ ርዕዩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ከሚያዝያ 30 እስከ ግንቦት 18፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከግንቦት 21 እስከ ሰኔ 1 እንዲሁም በሐያት ሪጀንሲ ሆቴል ከሰኔ 10 እስከ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ይቆያል ተብሏል፡፡

በታሪኩ ወልደሰንበት

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.