Fana: At a Speed of Life!

ትግራይን መልሶ የመገንባቱ ሥራ የድህረ ዘመቻ ዋናው ተግባራችን ነው- ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 26 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ትግራይን መልሶ የመገንባቱ ሥራ የድኅረ ዘመቻ ዋናው ተግባራችን ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ።

ይህ ተግባር ሦስት መልኮች አሉት ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

እነዚህም ሰብአዊና ማኅበራዊ ድጋፍ፣ የተጎዳውን መሠረተ ልማት መልሶ መገንባት እና መሠረታዊ አገልግሎቶችን መልሶ ማስጀመር መሆናቸውንም ገልጸዋል።

እነዚህ ሥራዎች በስፍራው በተገኙ ቡድኖች አማካኝነት ተጀምረዋልም ነው ያሉት።

የሰብአዊ ድጋፍ አገልግሎትም እጅግ ተጋላጭ የሆኑትን የማኅበረሰብ ክፍሎች በመደገፍ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

አንድ ሆነን የተቋረጠውን እናስቀጥላለን፣ የፈረሰውን እንገነባለን፣ የነገውንም እናለማለን ሲሉ በማህበራዊ ገጻቸው ገልጸዋል።

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
1,415
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.