Fana: At a Speed of Life!

የሴት ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ እንደ ሀገር ዝቅተኛ መሆኑ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሴት ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ እንደ ሀገር ዝቅተኛ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ነቢል መህዲ በአሁኑ ጊዜ የሴት ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ እንደ ሀገር ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሴት ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ከማምጣት ባሻገር በትምህርት ገበታቸው እንዲቆዩና ለውጤት እንዲበቁ አሁንም ትኩረት የሚሻ ጉዳይ መሆኑን እና የትምህርት ተቋማት ለሴት ተማሪዎች ምቹና ከትንኮሳ የፀዱ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑንም ነው የተናገሩት፡፡

በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ወሲባዊ፣ አካላዊና ስነ ልቦናዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ጥቃቶችን ለመቅረፍ ሁሉም ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣት ይገባዋል መባሉን ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.