Fana: At a Speed of Life!

የገንዘብ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችና ቀጠናዊ ደህንነት ዙሪያ ከኢጋድ ዋና ፀሃፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 6 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በአባል ሃገራቱ ውስጥ ማሻሻያዎችን እና ተቋማዊ አቅምን ማጠናከር በሚቻልበት አግባብ ላይ ተወያዩ፡፡

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ከኢጋድ ዋና ፀሃፊ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራሞች እና የአባል ሃገራቱን ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት አግባብ ላይ ተወያይተዋል፡፡

የገንዘብ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት በቀጠናው ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና በደህንነት ጉዳዮች ላይ ትስስርን በሚያጠናክር መልኩ ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ማጎልበት አስፈላጊ ስለመሆኑ አብራርተዋል፡፡

ትብብሩ ለሁሉም አባል ሃገራት ተጠቃሚነትና በተለይም ለአካባቢያዊ ሰላምና ደህንነት ወሳኝ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል፡፡

የኢጋድ ዋና ፀሃፊ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ በበኩላቸው የኢጋድን ፕሮግራሞች በአግባቡ ለመተግበር ተቋማዊ አቅምን መገንባት ያለውን ጠቀሜታ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

አያይዘውም ተቋሙ ለቀጠናው እድገትና መረጋጋት ከኢትዮጵያ ጋር በቅርበት መስራቱን ይቀጥላልም ብለዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.