Fana: At a Speed of Life!

በ34 ሚሊየን ብር የተገነባው የጉርሱም ሆስፒታል ስራ ጀመረ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 26፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ34 ሚሊየን ብር የተገነባው የጉርሱም ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተመርቆ ስራ ጀመረ።

ሆስፒታሉ የጤና አገልግሎትን አስመልክቶ ከዚህ ቀደም በአካባቢው ነዋሪዎች ሲቀርብ የነበረውን ቅሬታ እንደሚፈታ ታምኖበታል።

በኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ የሚመራው ልዑክ የጉርሱም ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን መርቆ ስራ አስጀምሯል።

መንግስት ለጤናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት ሰጥቶት እየሰራ ነው ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ፥ ዘርፉ የሚጠይቀውን አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ያስችል ዘንድ እንደ ጉርሱም ወረዳ ያሉ ሆስፒታሎች ወደ ስራ መግባታቸው አስፈላጊ ነው ብለዋል።

በነስሪ የሱፍ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.