Fana: At a Speed of Life!

በሀገር ውስጥና በውጭ ያለን ኢትዮጵያውያን አንድና ብዙ ሆነን በብዙ መስኮች ለማሳካት እንነሣ – ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 1፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በሀገር ውስጥና በውጭ ያለን ኢትዮጵያውያን አንድና ብዙ ሆነን በብዙ መስኮች ለማሳካት እንነሣ ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ‘‘ብዙ ሆነን፣ ብዙ ነገሮችን በብዙ መስኮች ለማሳካት እንነሣ’’ ብለዋል ።

‘‘በሀገር ውስጥና በውጭ ያለን ኢትዮጵያውያን፣ ሁላችንም ለኢትዮጵያ ከልብ ተነሥተን፣ የክረምቱን ግብርናና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ አረንጓዴ ዐሻራን፣ 2ኛው ዙር የሕዳሴ ግድብን ሙሌት፣ ሉዓላዊነታችንን ማስጠበቅን፣ ዲፕሎማሲያችንን፣ በአንድ ጊዜ፣ አንድና ብዙ ሆነን፣ በብዙ መስኮች ለማሳካት እንነሣ’’ ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.