Fana: At a Speed of Life!

የደቡብ ኦሞ ዞን ነዋሪዎች ለመከላከያ ሰራዊት ከ15 ሚሊየን ብር በላይ እና ሰንጋዎችን ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 12፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኙ ነዋሪዎች ለሀገር መከላከያ ሰራዊት 200 የሚጠጋ ሰንጋና ከ15 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድርገዋል።

ከየወረዳ እና ዞን ማዕከል የተሰበሰበቡ ሰንጋዎች ከጂንካ ከተማና ከወረዳ በተወጣጡ አመራሮች አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል።

ድጋፉ ጂንካ ከተማን ጨምሮ ሁሉም ወረዳዎች እያንዳንዳቸው ከ10 እስከ 30 የሚሆን ሠንጋ በማዋጣት ነው በግንባር ለሚዋደቁና የኢትዮጵያን ህልውና ለማስጠበቅ ለሚተጉ ሠራዊት አባላት የተበረከተው።

ሁሉም ወረዳዎች ከሃሰተኛ መረጃ እንዲቆጠቡ አሳስበበው የጠላት ሀሰተኛ መረጃ ሰለባ እንዳይሆኑ ÷ አንድነታችን ተጠናክሮ ወደ ብልጽግና ከፍታ እንወጣለን ሲሉ ነው የገለጹት።

ከሠንጋና ከገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ ወደ ግንባር ድረስ ለመዝመት ዝግጁ መሆናቸውን አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጋቱ ዳንሳ እንደገለፁት ÷ የዞኑ ማህብረሰብ 200 የሚጠጋ ሠንጋ፣ ከ15 ሚሊየን ብር በላይ ድጋ በተጨማሪ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የሚሆን የቀለብ ዝግጅት በማዘጋጀት ለሠራዊቱ እንዲደርስ ተደርጓል ማለታቸዉን ደሬቴድ ዘግቧል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.