Fana: At a Speed of Life!

የገንዘብ ሚኒስትሩ ከተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የምስራቅ አፍሪካ ልዩ ልዑክ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 17 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ ከተመድ የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን የምስራቅ አፍሪካ ልዩ ልዑክ አምባሳደር መሃመድ አብዲ አፌ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም ኢትዮጵያ የተለያዩ ሃገራት ስደተኞችን በማስተናገድ ረገድ እያከናወነች ያለውን ተግባር በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም በትግራይ ክልል እየተካሄደ ስላለው የሰብአዊ ድጋፍ መልሶ ግንባታ በተመለከተም ገለጻ አድርገውላቸዋል፡፡

ልዩ መልዕክተኛው መንግስት እያደረገ ያለውን ሰብአዊ ድጋፍ እንዲሁም የስደተኞችን ደህንነት ከመጠበቅ አኳያ መንግስት የወሰዳቸውን እርምጃዎችን አድንቀዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡-
https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.