Fana: At a Speed of Life!

ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ከሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ዋና ጸሃፊ ዶክተር ወርቅነህ ገበየው ከሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸውም የሶማሌ ክልል ከዚህ ቀደም አለመረጋጋት የሚስተዋልበት ክልል እንደነበር ዶክተር ወርቅነህ አስታውሰዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ችግሩ መቀረፉን የገለጹት ዋና ጸሃፊው ÷ ለሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ ያላቸውን አድናቆትም ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም በሀገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ሊሰሩባቸው በሚችሉ መንገዶች ላይ መምከራቸውን ዶክተር ወርቅነህ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡

በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ የተመራው ልዑክ ሄሪቴጅ ኢንስቲትዩት በተባለው ዓለም አቀፍ የጥናትና ምርምር ተቋም በተዘጋጀና ቀጠናዊ አጀንዳዎች ላይ በመከረ መድረክ ላይ ለመሳተፍ ነበር ወደ ጂቡቲ ያቀናው።

በሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ የተመራው ልዑክ ሄሪቴጅ ኢንስቲትዩት በተባለው ዓለም አቀፍ የጥናትና ምርምር ተቋም በተዘጋጀና ቀጠናዊ አጀንዳዎች ላይ በመከረ መድረክ ላይ ለመሳተፍ ነበር ወደ ጂቡቲ ያቀናው።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.