Fana: At a Speed of Life!

ሀገርን የሚያፈርሱ አጀንዳዎችን መመከት የሚቻለው አንድነትን ማጠናከር ሲቻል ነው – ምሁራን

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከውስጥ እና ከውጭ ኃይሎች የሚቀርቡ ሀገርን የሚያፈርሱ አጀንዳዎችን መመከት እና መከላከል የሚቻለው ሀገራዊ አንድነትን ማጠናከር ሲቻል ነው ሲሉ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁራን ተናገሩ፡፡
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት ምሁራን÷ ከውስጥ እና ከውጭ የሚቀርቡ አጀንዳዎች ሰላምን በማደፍረስ በኩል ሚናቸው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ አስተዳደር እና ልማት ተመራማሪ ዶክተር መሀመድ አሊ÷ ኢትዮጵያውያን አንድ የሚያደርጋቸው እሴቶች ስላላቸው ነው የመበታተን አጀንዳን እያከሸፉ ያሉት ብለዋል።
በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር ዶክተር ቃለወንጌል ምናለ÷ ለሀገር አንድነት እና ሰላም ፀር የሆኑ አጀንዳዎችን የሚያከሽፉ ትክክለኛ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ማድረስ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን የውስጣቸውን ጉዳይ በንግግር መፍታት ተስኗቸው ከፈረሱ ሀገሮች ታሪክ መማር ይኖርባቸዋል ብለዋል ምሁራኑ፡፡
በአልማዝ መኮንን
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.