Fana: At a Speed of Life!

ደብረ ብርሀን ዩኒቨርስቲ በአጣዬ እና አካባቢው ለተፈናቀሉ ወገኖች  ግምቱ ከ4 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)ከደብረ ብርሀን ዩኒቨርስቲ  የማህበረሰብ አካላት በአጣዬ እና አካባቢው ለተፈናቀሉ ወገኖች ግምቱ  ከ4ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የሚሆን ድጋፍ አደረገ።

ለተለያዩ የህክምና አገልግሎት የሚውሉ መድሀኒቶች ፣ ኮምፒዩተሮች፤ ወረቀቶች እና አልባሳት እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።

የደብረ ብርሀን ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ባዩ ጌታሁን÷  ዩኒቨርስቲው ከዚህ ቀደም በተለያዩ መሰል ድጋፎች ሲሳተፍ መቆየቱን አስታውሰው÷ በቀጣይም ባለው አቅም ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

ከተማሪዎች የተሰበሰበውን አልባሳት እና የጥሬ ገንዘብ በተወካይነት ያስረከቡት የዩኒቨርስቲው የተማሪዎች ህብረት ምክትል ፕሬዝዳንት ያሬድ ብርሀነ÷ ድጋፉ በአካባቢው ተከስቶ በነበረው ግጭት ለተጎዱት ተማሪዎች ከቁርሳቸው ቀንሰው ያሰባሰቡት እንዲሁም አልሳባቱ ከተማሪዎች በጎ ፈቃድ የተነገኘ መሆኑን ተናግረዋል።

የአጣዬ ከተማ ከንቲባ አቶ አገኘሁ መክቴ÷ የአጣዬ ከተማን ወደ ቀደመ እንቅስቃሴ ለመመለስ በአካባቢው ያሉ ተቋማት የዩኒቨርስቲውን ፈለግ መከተል ይገባቸዋል  ብለዋል

አያይዘውም የዩኒቨርስቲው ድጋፍ መሠረታዊ ችግሮችን ሊቀርፍ የሚችል መሆኑንም  ገልፀዋል።

በኤልያስ ሹምዬ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.