Fana: At a Speed of Life!

የወልቂጤ ከተማ እና የሲዳማ ቡናን የመሩት ረዳት ዳኛ ከውድድሩ ተሰናበቱ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የወልቂጤ ከተማ እና የሲዳማ ቡናን የመሩት ረዳት ዳኛ ዳንኤል ጥበቡ ከውድድሩ መሰናበታቸው ተገልጿል፡፡

በተጠናቀቀው የ13ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ወልቂጤ ከተማ እና ሲዳማ ቡና ባደረጉት ጨዋታ ላይ ረዳት ዳኛው ባሳዩት የዳኝነት ስህተት ነው ቅጣቱ የተላለፈባቸው፡፡

በዕለቱ ወልቂጤ ከተማ በመጀመሪያው አጋማሽ በአማካዩ በሀይሉ ተሻገር አማካኝነት ግብ ያስቆጠረ ቢሆንም÷ ረዳት ዳኛ ኳሱ ከጫዋታ ውጭ ነዉ ማለታቸውን ተከትሎ ጎሉ ሳይፀድቅ ቀርቷል፡፡

ይሁን እንጂ ጎሉ ከጨዋታ ውጭ አለመሆኑ በዳኞች ኮሚቴ ከተረጋገጠ በኋላ ኮሚቴዉ የዕለቱ ረዳት ዳኛ ዳንኤል ጥበቡ በፈፀሙት የዳኝነት ስህትት ከውድድሩ በማገድ ከድሬዳዋ አሰናብቷቸዋል፡፡

 

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.