በኦስሎ የ5 ሺህ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቀዋል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦስሎ ከተማ በ5ሺህ ሜትር የተካሄደውን የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች በበላይነት አጠናቀዋል፡፡
በወንዶች ምድብ በተካሄደው 5 ሺህ ሜትር የኦስሎ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ጥላሁን ሃይሌ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ÷ ሳሙኤል ተፈራ እና ጌትነት ዋሌ 2ኛ እና 3ኛ ሆኖ በመግባት ውድድሩን ጨርሰዋል።
በተመሳሳይ በሴቶች ምድብ በተካሄደው የ5 ሺህ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር ዳዊት ስዩም ርቀቱን በቀዳሚነት ስታጠናቅቅ÷ ጉዳፍ ጸጋይ እና ለተሰንበት ግደይ ደግሞ 2ኛ እና 3ኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቀዋል፡፡
በተጨማሪም በምድቡ አትሌት ሚልኬሳ መንገሻ 5ኛ፣ አሊ አብዱልመናን 10ኛ ሆነው ማጠናቀቃቸውን ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡