Fana: At a Speed of Life!

በፕሪሚየር ሊጉ ሀዲያ ሆሳዕና እና አዳማ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሁለተኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀዲያ ሆሳዕና እና አዳማ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል፡፡

ዛሬ ምሳ ሰዓትና ከከሰዓት በኋላ ሁለት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡

በዚህም 7 ሰዓት ሀዲያ ሆሳዕና ከሲዳማ ቡና ጨዋታቸውን ያደረጉ ሲሆን÷ ሀዲያ ሆሳዕና 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

የሀዲያ ሆሳዕናን የአሸናፊነት ጎሎች ፍቅረየሱስ ተወልደብርሀን፣ብሩክ ማርቆስ፣ ፀጋዬ ብርሀኑ እና ባዬ ገዛኸኝ ሲያስቆጥሩ ሲዳማ ቡናን ከሽንፈት ያልታደገችውን ግብ ያኩቡ መሐመድ አስቆጥሯል፡፡

10 ሰዓት መቻል ከአዳማ ከተማ ያደረጉት ጨዋታ በአዳማ ከተማ 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡

የአዳማ ከተማን ግቦች ዳዋ ሆቴሳና አሜ መሃመድ አስቆጥረዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.