Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ ከኮቲዲቯር ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ ከኮቲዲቯር ፕሬዚዳንት አላሳኔ ኦታራ ጋር ተወያይተዋል፡፡
 
ፕሬዚዳንቶቹ በውይይታቸው በኢትዮጵያ እና ኮቲዲቯር መካከል በተለያዩ ዘርፎች ላለው ጠንካራ ትብብር እውቅና ሰጥተዋል፡፡
 
በቀጣይም በሀገራቱ መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በተመሳሳይ ፕሬዚደንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ÷ የአፍሪካ ልማት ባንክ በአቢጃን ኮቲዲቯር በተዘጋጀው የአፍሪካ ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ተሳትፈዋል፡፡

በችግር ጊዜ መልካም አጋጣሚዎች መኖራቸውን የጠቀሱት ፕሬዚዳንቷ÷ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በባንኩ ድጋፍ በስንዴ ምርት በኢትዮጵያ ስለተገኘው  ውጤት አብራርተዋል፡፡

ኮቲዲቯር በተመድ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ለኢትዮጵያ ለሰጠችው ድጋፍ ማመስገናቸውን የፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

 

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.