Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያና ጣሊያን በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በትብብር መሥራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሥራና ክኅሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል በኢትዮጵያ ከጣሊያን አምባሳደር አጎስቲኖ ፓሌሴ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በኢትዮጵያ እና ጣሊያን መካከል በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና በትብብር መሥራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን በኢትዮጵያ የጣሊያን ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

በተጨማሪም የእውቀት ሽግግር ማድረግ ስለሚቻልበት ሁኔታ፣ የልማት ማዕከላትን ስለመገንባት እንዲሁም በሌሎች የትብብር መስኮች ላይ መወያየታቸው ተገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.