Fana: At a Speed of Life!

የፕሪሚየር ሊጉ 7ኛ ሳምንት ቀሪ 4 ጨዋታዎች ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘሙ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 3 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ7ኛ ሳምንት ቀሪ 4 ጨዋታዎች ላልተወሰነ ጊዜ መራዘማቸው ተገለጸ።

ጨዋታዎቹ በድሬዳዋ ወቅታዊ የአየር ንብረት ምክንያት የመጫወቻ ሜዳው ለማጫወት ምቹ ባለመሆኑ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘማቸው ተገልጿል።

በዚህ መሰረት ዛሬ እና ነገ የሚካሄዱ ጨዋታዎች መራዘማቸውን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል።

የተራዘሙት ጨዋታዎች ዛሬ 10:00 ሰዓት አርባምንጭ ከተማ – ከባህርዳር ከተማ
1:00 ሰዓት ሀዲያ ሆሳዕና – ከፋሲል ከነማ እንዲሁም

ነገ 10:00 ሰዓት አዳማ ከተማ – ከኢትዮጵያ ቡና

1፡00 ሰዓት ለገጣፎ ለገዳዲ – ከወላይታ ድቻ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ተራዝመዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.