Fana: At a Speed of Life!

በይነመረብን ከምድራችን ውጭም በመዘርጋት መጠቀም ይኖርብናል- የኢንተርኔት አባት

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የበይነመረብ ግንኙነትን ከምድራችን ውጭ ባሉ ቦታዎች በመዘርጋት መጠቀም ይኖርብናል ሲሉ የኢንተርኔት አባት በመባል የሚታወቁት ቪንቶን ሰርፍ ተናገሩ።

በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው 17ኛው ዓለም አቀፉ የበይነ መረብ አስተዳደር ጉባዔ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት ቪንቶን ሰርፍ ስለ በይነ መረብ አስተዳደር እና የወደፊት እጣ ፋንታ ምልከታቸውን አጋርተዋል።

በበይነ መረብ ግንኙነት ውስጥ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት አዲስ ዓለም ውስጥ እየገባን በመሆኑ የበይነመረብ ግንኙነቶች ሊያሟሏቸው ስለሚገቡ መስፈርቶች ማሰብ ይገባል ብለዋል፡፡

በይነመረብን ለበለጠ ልማት ስራ ላያ ለማዋል አሁን ከምንኖርበት ምድር ውጭ ባሉ ሌሎች ፕላኔቶች መዘርጋት ይኖርብናል ነው ያሉት።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.