ከ20 ዓመት በታች በ5ሺህ ሜትር ሴቶች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1 እስከ 3 በመውጣት ድል አደረጉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛምቢያ ንዶላ ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ማጠቃለያ ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1 እስከ 3 በመውጣት ድል አድርገዋል፡፡
አትሌት ውብርስት አስቻለ ቀዳሚ በመሆን ለሀገሯ ወርቅ ስታስገኝ፣ አይናዲስ መብራቴ 2ኛ በውጣት ብር እንዲሁም አስማረች አንለይ 3ኛ በውጣት ነሃስ አስገኝተዋል፡፡
በውድድሩ ኢትዮጵያ 7 የወርቅ በአጠቃላይ ደግሞ 23 ሜዳሊያዎችን መሰብሰብ ችላለች፡፡