Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ከፍ ትላለች እንጂ ሞት አያገኛትም- ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከትንሳኤ በኋላ ዳግም ሞት እንደሌለ፤ ኢትዮጵያም ከዚህ በኋላ ከፍ ከፍ ትላለች እንጂ ሞት ዳግም አያገኛትም ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የትንሳኤ በዓልን አስመልክተው ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት÷ ትንሳኤ ሞትንና መቃብርን የማሸነፍ በዓል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የክርስቶስ መነሳት ተዘግቶ የሚቀር ነገር እንደሌለ ከሞት ወዲያ ሕይወት፣ ከመቃብር ወዲያ ትንሳኤ መኖሩን አስተምሮናል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ኢትዮጵያም አለቀች፣ ደቀቀች፣ ተጠናቀቀች፣ ሞተች፣ ተቀበረች ያሏትን ሁሉ አሳፍራ እየተነሳች ነው፤ መግነዟን ፈትታ፣ ሞቷን ድል ነስታ፣ መቃብሯን ትታ በሁሉም ነገሯ እየተነሣች ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡

ከትንሳኤ በኋላ ዳግም ሞት እንደሌለ፤ ኢትዮጵያም ከዚህ በኋላ ከፍ ከፍ ትላለች እንጂ ሞት ዳግም አያገኛትም ሲሉም አስረድተዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.