በፕሪሚየር ሊጉ ባህር ዳር ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቷቸዋል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባህር ዳር ከተማ እና ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቷቸዋል፡፡
በዛሬው እለት በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በ24ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መርሐ ግብር ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡
በዚህም ቀን 9 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ጨዋታቸውን ያደረጉ ሲሆን÷ ኢትዮጵያ ቡና ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግብ ሮቤል ተ/ሚካኤል 52ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
በተመሳሳይ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ባህር ዳር ከተማ አዳማ ከተማን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
አደም አባስ የማሸነፊያ ግቧን 79ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡