Fana: At a Speed of Life!

ድሬ ጎዳና ሆስፒታል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ109 ሚሊየን ብር ወጪ በአዳማ የተገነባው የድሬ ጎዳና ሆስፒታል በዛሬው ዕለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡

ሆስፒታሉ ዘመናዊ የሕክምና መሣሪያዎች የተሟሉለት ሲሆን፥ በሰው ኃይልም በበርካታ ስፔሻሊስት ሐኪሞች የተደራጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የጤና አገልግሎት ተቋሙ ሥራ የተጀመረው መሠረታዊ የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ማድረግን ዓላማ በማድረግ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

የጤና አገልግሎትን በሁሉም ቦታ ለሁሉም ለማዳረስ በሚል ከ11 ዓመታት በፊት በክሊኒክነት ሥራውን የጀመረው የጤና ተቋም ነው አሁን ወደ ሆስፒታልነት ያደገው።

በትዕግሥት ብርሃኔ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.